ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል!!

“ለ አይ አር ኤስ (IRS) በእጃችን ያለውን ማስረጃ አስረክበን ቤተክርስቲያኑን እናዘጋዋለን! መንግስት እንዲወርሰው እናደርጋለን! በኋላ ለምን እንዲህ አደረጋችሁ እንዳትሉን!” በሚል ርእስ ሰላም ተዋህዶ በሚባለው የማህበረ ቅዱሳን ድረገጽ (ዌብሳይት) ተቀጥላ ብሎግ ላይ የተጻፈ የዘለፋና የማስፈራሪያ ጽሁፍ ሲሆን፤ እውነትም የሚካኤል ጠላቶች የገመዳቸው ጫፍ ላይ መድረሳቸውን ከጽሁፉ በግልጽ መረዳት ይቻላል።

ደራሲው ሲዘግብ ሁለት የሚካኤል ቤተክርስቲያን አባል ከሆኑና የማህበረ ቅዱሳን የቅርብ ወዳጅ ከሆኑ ግለሰቦች ሪፖርቱን ያገኘ መሆኑን ገልጿል። እንዴ? እንዲህ ያሉ ሊቆች፤ ሊቀ ሊቃውንት፤ ከወዴት ተገኙ? አይ ሞኙ! ተላሌ! የትኞቹ አንኮላዎች ናቸው ይህችን የሞኞች የማጭበርበሪያ ዘዴ ሲሞሉህ የከረሙት? ሁለት ያልካቸውስ የቤተክርስቲያን ተቆርቋሪዎች፤ እነማን ይሆኑ?
ጭቃን አድርቆ ተሻሻለ ማለት ዝናብ እስቲዘንብ ድረስ ነው።
ሰላም ተዋህዶ ለህዝብ የተቆረቆረ መስሎ ሰሞኑን ታይቶ ነበር። እኛም እውነት ለመልካም ተግባርና ቤተ ክርስቲያንና ምእመኑን ለማፋቀር የቆመ መስሎን ማመስገን ጀምረን ነበር! ለካስ መልሶ ጭቃ ለመሆን የሚጠብቀው ዝናብ ነበር።

የደጀሰላም ድረገጽ፤ የሐመር እና የስምአጽድቅ ኤዲተር የሆነው በዲሲ ከተማ በግዞት ላይ የሚገኘው የማህበረ ሰይጣን ባልደረባ እና የሚካኤል ሰይፍ የሚያስልፈልፋቸውና የሚያክለፈልፋቸው እኩያን አሳሳቾች እብዙ ውሸት መሀል ትንሽ እውነት በመደብለቅ ሰላምተዋህዶ የሚል ብሎግ ከፍተው ህዝብን ለማሳሳት የሚያደርጉት ጥረት እርቃኑን ስለወጣ አዚማቸው አልይዝ ብሎ ውርደታቸውን እየተጎናጸፉ ይገኛሉ።

የከሳሾች ብሎግ ደግሞ መረዋመታ የሚል ስም ተሰጥቶት እንደመዥገር ተጣብቀው የቤተክርስቲያንን ሀብትና ንብረት ለአመታት ሲዘርፉ የኖሩት እነተኮላ፤ በቀለ፤ ነጋሽ፤ መስፍን ወዘተ፤ ከነግብረአበሮቻቸው ዛሬ የቤተክርስቲያን ሃሳቢ በመመሰል የመሸታ ቤት አሉባልታቸውን አፋቸውን ሞልተው ለማውራትና ለመዘገብ በቅተዋል። እነዚህ የአርዮስ ልጆች ለሚካኤል ቤተክርስቲያን ጓዳቸውን የቀድሞ ሊቀመንበር ለመጥቀስ “ለሚጠጡት ሻይና ለሚበሉት ዳቦ ያህል እንኳን ስሙኒ የማይሰጡ” ሲሆኑ አባል ላልሆኑለት ቤተክርስቲያን አሳቢ በመምሰል እንዳይዘርፉ ያስቆሟቸውን ሁሉ በመወንጀልና ስም በመስጠት ይኮንናሉ። የነዚህን ሌቦች ተግባር በዝርዝር የሚያውቁት የሚካኤል ቤተክርስቲያን አባላትም አንቅረው አክ እንትፍ ብለዋቸዋል።
ትእግስት ፍርሃት እንዳልሆነ ያልተረዳ ህዝብ አወዳደቁ የከፋ ይሆናል!!
 የተከበራችሁ የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል አባላት ሆይ!!

የዚህችን ቤተክርስቲያን ጠላቶች ሴራና እኩይ አላማ ከነተግባራቸው በግልጽ ሕዝቡ እንዲያውቅ ለማድረግ ስናስብ ይፋ የሚወጡበትን እና እርቃናቸውን የሚቀሩበትን ወቅት በራሳቸው ጥያቄ ስላመጡት ለሕዝቡ ማሳወቅ ግዴታ ሆኖ አግኝተነዋል። እስከመቼ ተለባብሰው እሹሩሩ እየተባሉ ይኖራሉ? ሕግ በሌለበት አገር ወንጀል ሲፈጽሙ ኖረው፤ ከዛ አምልጠው እዚህ ሕግ ያለበት አገር መጥተው ደግሞ የሚያውቀን የለም በሚል በየቤተክርስቲያኑ መሽገው ኖሩ።

የወንጀለኛው ቁጥር እየጨመረ በሄደ ቁጥር በሽታቸው እያገረሸ ስለመጣ የተለመደውን ተግባራቸውን በእግዚአብሔር ቤት መለማመድ ቀጠሉ። ሃይ የሚላቸውም ስለጠፋ ጎለበቱ። ጠያቂ ሲነሳም የሌለውን ታሪክ ሰጥተው አዋርደውና አበሻቅጠው ያባርሩታል። ይኸም ድርጊት ያለቁጥጥር የወንጀል መረባቸውን እንዲዘረጉና ተዝናንተው ይህችን ቤተክርስቲያን እንደመዥገር ተጣብቀው ደሟን እንዲመጡ እድል ሰጥቷቸዋል። ሆኖም በማንአለብኝነት ስለታበዩ ጥጋቡ ገፈተራቸውና ሕዝቡን ከመናቅ አልፈው እግዚአብሔርን መዳፈር ጀመሩ። ስለዚህም ነው ጉዳቸው የአደባባይ ምስጢር እየሆነ የመጣው። የእግዚአብሔርን ቤት ስላረከሱና ሰይጣናዊ ተግባራቸውን ሃይማኖተኛ በመምሰል በመቅደስ ሳይቀር በመተግበር በእግዚአብሔር መንፈስ ላይ ስለቀለዱ፤ ስሙን በከንቱ ከሚጠሩት ከሰራዊት ጌታ የእጃቸውን መቀበያው ወቅት ተቃረበ። ታድያ ከእግዚአብሔር መደበቅ ይቻል ይሆን?